እየተካሄደ በሚገኘው የኮንሶ ምሁራን ማህበር 4ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ የክረምት በጎ ተግባር እየተከናወ ነው፣
- basire balcha
- 2 days ago
- 1 min read
እየተካሄደ በሚገኘው የኮንሶ ምሁራን ማህበር 4ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ የክረምት በጎ ተግባር እየተከናወ ነው፣
በመካሄድ ላይ በሚገኘው የምሁራን ማህበር 4ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ የክረምት በጎ አካል የሆኑ የደም ልገሣ መርሃግብር እየተካሄደ ነው።
የኮንሶ ዞን ከፍተኛ አመራሮች በወቅቱ እንደገለጹት ደም መለገስ ሊተካ በሚችል ደም ሊተካ የማይችል ህይወትን የማዳን ኃላፊነታችንን እየተወጣን ነው ሲሉ ገልጸው ሁሉም በዚህ በጎ ተግባር የበኩሉን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።
በጎ ማድረግ የጽድቅ ስራና የመልካምነት መገለጫ መሆኑን ያስገነዘቡት የዞኑ ከፍተኛ አመራሮቹ፤ለበጎነት እጃችንን በመዘርጋት ድጋፍ ለሚሹ አካላት የድርሻችንን ሊንወጣ ይገባልም ብለው የደም ልገሳ መርሃግብር እንደሚቀጥልም ተመላክቷል።
ካራት:ነሐሴ:22/2018 ዓ.ም
(ኮንሶ ዞን ኮሙኒኬሽን)


Comments